Home

ወደ ዋና ገጻችን እንኳን በደህና መጡ!

Welcome to our church web site!

ካቴድራላችን ላለፉት ሁለት አስርት ዓመታት ሲጠቀምበት የነበረውን መተዳደሪያ ደንብ በአዲስ ለመቀየር እና የሚቀጥሉትን ሰበካ ጉባኤ አባላት መርጦ ለማስረከብ እየሰራ ይገኛል። በዚህ ሂደት የካቴድራላችን አባላት ንቁ ተሳታፊ በመሆን በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ሁለት ዙር አስተያየት በመስጠት ላደረጉት ትብብር ምስጋና እያቀረበ የቀረበውን የመጨረሻ ድራፍት ባይሎ ከዚህ በታች ያለውን መጠቆሚያ በመጫን ማግኘት እንደሚችሉ እናሳስባለን። መተዳደሪያ ደንቡን ለማጽደቅ የቀረው አንድ የመጨረሻ ሃሳብ ላይ ተወያይቶ እና ድምጽ ሰጥቶ ውሳኔ ማስተላለፍ ሲሆን ተጨማሪ ያልተካተቱ ጠቃሚ ሕጎች ይኖራሉ ብለው የሚያምኑ ከሆነ ሃሳቦትን info@kidusmichaeldc.org ኢሜል አድራሻ መላክ ይችላሉ።

Click on the picture to download draft bylaw

 

Donate

ቤተ ክርስቲያናችን የመኪና መቆሚያ ማስፋፊያ እና ተጨማሪ ሦስት አሮጌ ቤቶች ያሉበት ግማሽ ኤከር መሬት በ2.9 ሚሊዮን ዶላር ገዝቶ በወር 15 ሺ ዶላር ሞርጌጅ እየከፈለ ሲሆን ቤቶቹን በፍጥነት አሳድሶ የልጆች ማስተማሪያ ሁለገብ አዳራሽ ለመገንባት ያስባል። ይህንን ጥረት ለማገዝ የሚችሉትን ሁሉ እንዲያደርጉ አደራ እንላለን።

ለቤተ ክርስቲያናችን አባላት እና ምዕመናን ለቤተ ክርስቲያን ስጦታ ፣ መባ ፣ አስራት ወይም ስለት ኦን ላይን መስጠት ከፈለጉ ከዚህ በታች ያለውን “ለቤተ ክርስቲያኑ ይለግሱ” የሚለውን ቁልፍ በመጫን ወደ ስኴር የመክፈያ በመሄድ የአቅሞትን መለገስ ይችላሉ።

ሰላም የእግዚአብሔር ቤተሰቦች

እግዚአብሔር ረድቶን ባለፈው ዓመት ለፋሲካ አንድ ኩንታል (a quintal for Fasika) የሚል ዘመቻ ተጀምሮ ከ$36,000 በላይ ሰብስበን ከግማሽ ሚሊዮን ኩንታል በላይ እህል ከቅዱስ ሚካኤል በጎ አድራጎት ከየቦታው: ተፈናቅለው: በደብረ ብርሃን ለሰፈሩት ተፈናቃዮች ተበርክቷል:: 

እንዳውም ትርፍ ገንዘብ ኖሮን: 5 ለእርድ የሚሆኑ በሬዎችን: ዘይት: እና: 500 ብርድ ልብሶች: በጎ አድራጎት: አስረክቧል::

በአሁኑ ሰዓት ችግሩ በጣም የተባባሰ ቢሆንም: በዚህ ዓመትም እንዳለፈው  ዓመት አንድ ኩንታል ለፋሲካ እንድታበረክቱልን የቅዱስ ሚካኤል በጎ አድራጎት ክፍል በአክብሮት ይጠይቃል

አንድ ኩንታል ለማትችሉ ግማሽ ኩንታል መለገስ ትችላላችሁ 

ጤፍ – $130 
በሶ –  $140
ምጥን ሽሮ – $140
ስኳር $130
ስንዴ – $100
ሽንብራ – $100
ብርድ ልብስ – $40

እርዳዋትን ከዚህ በታች ያለውን ስኵር ሊንክ በመጠቀም መላክ ይችላሉ።

About

Our Mission is :

To uphold the centuries-old tradition and values of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church; to increase the awareness of our community about the history, cultures, languages, and tradition of Ethiopia; and to provide other social services consistent with our religious practices.

News

፳፻፲፮ ዓ.ም (2023-2024) ዘመን የሃይማኖት ትምህርትና የአማርኛ ቋንቋ ትምህርት ምዝገባ

ነባርም ሆነ አዳዲስ ተማሪዎች መመዝገብ ይኖርባቸዋል ከ4 ዓመት ዕድሜ ጀምሮ ያሉ ልጆችን ለትምህርት እንቀበላለን ከአንድ በላይ ልጅ የሚያስመዘግቡ ከሆነ ለእያንዳንዱ ልጅ የተለያየ ቅጽ ይሙሉ። አንድ ቅጽ ለአንድ ልጅ ከአንደኛ ክፍል ጀምሮ ላሉ ተማሪዎች በሙሉ ትምህርት የሚሰጠው በሳምንት ሁለት ቀን ሲሆን ቅዳሜ እና እሑድ የሚኖሩን ክፍሎች (ትምህርቶች) በሙሉ የሚሰጡት በአካል በደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ይሆናል።  Pre-K and KG …

የቦታው ግዢ በስኬት ተጠናቀቀ

ከሐምሌ መጀመሪያ ጀምሮ ከፍተኛ ጥረት ሲደረግበት የነበረው ከቤተ ክርስቲያናችን ጎን ያለውን የፓርኪንግ ቦታ እና ቤቶች የመግዛት ሂደት ረቡዕ ኅዳር ፳፩ በእመቤታችን ዕለት በስኬት ተጠናቋል። የዲሲ እና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ፋኑኤል ፣ የሰበካ ጉባኤው አባላት ፣ የማውንት ኮሬብ ባፕቲስት ቸርቺ ቦርድ አባላት እና የሁለቱም የሪል ስቴት ባለሙያዎች በተገኙበት በዋሽንግተን ዲሲ ዲስትሪከት ታይትል …

ለሚገዛው ቦታ ፈንድሬዚንግ

ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል (ዋሽንግተን ዲሲ)ከቤተ ክርስቲያኑ ጎን ለሽያጭ የወጣውን የፓርኪንግ ቦታ እና ሦስት ቤቶች ከ፫ ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ አድርጎ ለመግዛት እያደረገ ላለው ጥረት የተዘጋጀ ፈንድሬዚንግ ነው። ከማክሰኞ ኅዳር ፮ (November 15) ጀምሮ በፌስ ቡክ ዶኔሽን ወርሃዊ ክፍያ ለሚያደርጉ ፌስ ቡክ ሁለተኛ ክፍያቸውን እስከ መቶ ዶላር ድረስ እጥፍ(ማች) በማድረግ ይሰጣል። ስለዚህ በወር እስከ …

Contact

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተ ክርስቲያን
አድራሻችን

3010 Earl Pl NE,
Washington, DC 20018

ሳምንታዊ መርሃ ግብር
6:00 – 9:30 የኪዳንና ቅዳሴ ጸሎት
ከ9:30 – 11:00 ስብከተ ወንጌል
ከ12:00 – 1:30 ሰንበት ትምህርት ቤት መርሃ ግብር

የጥምቀት ፣ የተክሊል ፣ የፍትሐት ወዘተ አገልግሎት ማግኘት ከፈለጉ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከ 9:00 – 4:00 በስልክ ቁጥር 202-529-7077 ይደውሉ።

 

የሕዝብ ግንኙነት ክፍልን ማግኘት ከፈለጋችሁ 240-308-8903 ይደውሉ።